የአርቲስት ሒሩት በቀለ ስርዓተ ቀብር በዛሬው እለት ይፈጸማል፡፡
የአርቲስት ሒሩት በቀለ ስርዓተ ቀብር ዛሬ ሰኞ ግንቦት 7 ቀን 2015ዓ.ም ጉለሌ በሚገኘው ጴጥሮስ ወጳውሎስ መካነ መቃብር ይፈፀማል።
አስከሬኗ ወደ ወዳጅነት አደባባይ አያመራም። ምክንያቱም የፕሮግራም ለውጥ ተደርጓል። በዚህ መሰረት በሀገር ፍቅር ቴአትር አዲስ መርሐ-ግብር ተዘጋጅቷል።
በሀገር ፍቅር ቴአትር በሚኖረው መርሐ-ግብር መሰረት
* በመሰረተ ክርስቶስ ቤተ-ክርስቲያን አማካኝነት የጸሎት ስነ ስርዓት ይካሄዳል፣
* የህይወት ታሪክ በንባብ ይሰማል
* የአበባ ማስቀመጥና
* የታዋቂ ሰዎች ንግግር ይደረጋል ተብሏል።
በመጨረሻም ከቀኑ 7፡00 ሰዓት ጉለሌ በሚገኘው ጴጥሮስ ወጳውሎስ መካነ መቃብር ስርዓተ ቀብሯ እንደሚፈጸም ተነግሯል።
ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን
ግንቦት 07 ቀን 2015 ዓ.ም
ለታማኝና ወቅታዊ መረጃዎች ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።
Telegram https://t.me/ethiofm107dot8
YouTube https://www.youtube.com/…/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos
Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast
Website https://ethiofm107.com/
ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።
ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።