
የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያ የእርስ በርስ ጦርነቱ ምክንያት የሻከረውን ግንኙነት የማሻሽለው “ቀስ በቀስ፤ ደረጃ በደረጃ” ነው አለ። የአውሮፓ ኅብረት የውጭ ጉዳዮች ከፍተኛ ተወካይ ጆሴፍ ቦሬል ኅብረቱ ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን ግንኙነት የሚያሻሽለው በጊዜ ሂደት መሆኑን ተናግረዋል። ቦሬል ይህን ያሉት ከአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አንቶኒ ብሊንከን ጋር በአሜሪካ እና ኅብረቱ መካከል ስላለው ግንኙነት ብራሰልስ ውስጥ ውይይት ካደረጉ በኋላ ነው።
Source: Link to the Post