የአየር ንብረት ለዉጥ ከቁጥጥር ዉጭ ሊሆን መቃረቡን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስታወቀ፡፡
ዓለም የአየር ንብረት ለዉጥን በፍጥነት መዋጋት ካልቻለች፣ በቅርብ ጊዚያት ዉስጥ ከቁጥጥሯ ዉጭ እንደሚሆን ድርጅቱ አሳስቧል፡፡
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀኃፊ አንቶንዮ ጉተሬዝ የአየር ንብረት ለዉጥ አደገኛ ደረጃ ላይ ደርሷል ብለዋል፡፡
ዓለም ለችግሩ ትኩረት ሰጥታ አስቸኳይ መፍትሄ ካልፈለገችለት ሁኔታዉ የከፋ እንደሚሆንም የድርጅቱ ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ አሳስበዋል፡፡
የዓለም የበረዶ ግግሮች በፍጥነት እየቀለጡ መሆናቸዉንም የድርጅቱ ሪፖርት አመላክቷል ሲል ሲ ኤን ኤን ዘግቧል፡፡
በአባቱ መረቀ
መጋቢት 12 ቀን 2015 ዓ.ም
ለተጨማሪ መረጃዎች የቴሌግራምና የዩቲዩብ ቻናሎቻችንን ይቀላቀሉ!
Telegram https://t.me/ethiofm107dot8
YouTube https://www.youtube.com/@onelovebroadcast
ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።
ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን