የአፍካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ በሰላም ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ አስፈላጊው ዝግጅት ተጠናቋል…የአዲስ አበባ ፓሊስየህብረቱ ጉባኤ ያለአንዳች ችግር በሰላም እንዲጠናቀቅ ሰፊ ዝግጅት መደረጉን የአ…

https://cdn4.telegram-cdn.org/file/cA9Y8srMRdBY-OLZg0oUWjcUCOUUroWIuzMJYiWzL-R6EfJiBFNXdZ0jq3cbSYdPvFeb69epMkBNGKpAg3aP0O9GZ_fIYJPx3vrkKGqZQ3NlwtO6MYbafDNuN4UOBqqBO0NtK6lV0Glkfit4ldkDYm53m3BxyyrhjqE9ZPWmwuKg5t0aiG6oTbljOd_0H85ubwCg1Xky7VJozYpPbckn7iZ1xXdimpB_TwXStbeq7I8z3_O40aljOrXAJSom5JhjzUrlJj0yD7wqIyFabF6OR07WQLYVhARVDl_18MTXGMWdVT_cVv_pi-voNvSvplBW1I9MncTRMi84HJHDlskb-Q.jpg

የአፍካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ በሰላም ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ አስፈላጊው ዝግጅት ተጠናቋል…የአዲስ አበባ ፓሊስ

የህብረቱ ጉባኤ ያለአንዳች ችግር በሰላም እንዲጠናቀቅ ሰፊ ዝግጅት መደረጉን የአዲስ አበባ ፓሊስ ኮምሽን አስታውቋል፡፡
የአዲስ አበባ ፓሊስ ኮምሽን የህዝብ ግንኙነት ዳሬክቶሬት ዳሬክተር ም/ኮ ማርቆስ ታደሰ ለኢትዮ ኤፍኤም እንደተናገሩት፣ ፓሊስ የህበረቱ ጉባኤ ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ ሰፊ ስራዎች መስራታቸውን ነግረውናል፡፡

ከዚሁ ጋር ተያይዞ ባለፉት ቀናትም ወታደራዊ የተግባር ልምምዶች ተካሂደዋል ብለዋል፡፡
የእንግዳ ማረፊያዎችን ጨምሮ ከፀጥታ፤ከትራፊክ እና ከወንጀል አንፃር ሊያጋጥሙ የሚችሉ ሁኔታዎችን በማጥናት፣ የሞተር ሳይክል እና ሌሎችም ተመሳሳይ እንቅስቃሴዎች ገደብ ሊጣልባቸው እንደቻለ ገልጸዋል፡፡

በተመሳሳይ የእንግዳ ማረፊያ ባለቤቶች በዚህ ወቅት የሚቀበሏቸውን እንግዶች ማንነት አስቀድሞ ማወቅና ህብረተሰቡንም አካባቢውን ነቅቶ መከታተል እንዳለበት፣የሚያጠራጥሩ ሁኔታዎች ሲያጋጥሙም ለአካባቢ ፓሊስ መጠቆም እንደሚገባም አስታውቀዋል፡፡

ለእንግዶች ቅድሚያ በመስጠት የትራፊክ ፓሊስ አባሎችን ትእዛዝ በማክበር፤ በጉባኤው ሊዘጉ የሚችሉ መንገዶችን ታሳቢ በማድረግ ህብረተሰቡ ቀና ትብብር እንዲያደርግም ጥሪ ቀርቧል፡፡

በየውልሰው ገዝሙ

የካቲት 06 ቀን 2015 ዓ.ም

Source: Link to the Post

Leave a Reply