የኢትየጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን ባለፉት ስድስት ወራት የነበረው የስራ አፈጻጸም ከ90 በመቶ በላይ መሆኑን ገለጸ።
የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽ ስራዎች ኮርፖሬሽን የስድስት ወራት አጠቃላይ የሥራ አሰፈፃፀም 90.3 ደርሶል ሲል ዛሬ በሰጠው መግለጫ ገልፃል፡፡
ኮርፖሬሽኑ የግማሽ ዓመት የገቢ መጠኑ 3.20 ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱን የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጅነር ዮናስ አያሌው ገልፀዋል፡፡
የ2015 በጀት ዓመት የስድስት ወር አፈፃፀሙ ያቀረቡት ኢ/ር ዮናስ በተጠቀሰወስ በጀት ዓመት 30 የህንፃ ግንባታ ፕሮጀክቶች፣23 የመንገድና ድልድልይ ግንባታ ፕሮጀክቶች፣ እና 8 የውሃ ኃብት ልማት ግንባታ ፕሮጀክቶች በአጠቃላይ 62 ፕሮጀክቶች ከ45.2 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ የኮንትራክት ዋጋ እየተከናወነ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡
የህነፃ ግንባታ ፕሮጀክት የስራ አፈፃፀም 107 በመቶ፣የመንገድና ድልድይ ግንባታ ፕሮጀክት 67.9 በመቶ የውሃ ኃብት ልማት ፕሮጀክት 99 በመቶ እንዲሁም የቤት ልማት ግንባታ ፕሮክቶች የስራ አፈፃፀም 87.37 በመቶ እንደሆነም ተገልፃል፡፡
እንደ ኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፋፃሚ ገለፃም ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ 599.5 ኩንታል የግብርና ምርት ማምረቱን ገልፀዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን በርካታ የሪፎርም ስራዎች እያከናወነ እንደሚገኝና የለውጥ አምጪ መሳሪያዎችን እንደ አይ ኤስ ኦ እና ካይዘን ትግበራ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ተገልፃል፡፡
በአቤል ደጀኔ
የካቲት 04 ቀን 2015 ዓ.ም