የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን ጉዳይ የሚከታተለው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሁለተኛ መሠረታዊ መብቶች እና ነጻነቶች ምድብ ችሎት የዕግድ ትዕዛዝ መስጠቱ ተገለፀ።
ፍርድ ቤቱ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የእግድ አቤቱታ መሠረት ቤተ ክርስቲያኗ አውግዛ በለየቻቸው ተጠሪዎች ላይ የእግድ ትእዛዝ መስጠቱን የቤተክርስቲያኗ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
በዚህ ጉዳይ የቤተክርስቲያኗ የህግ ክፍል ዝርዝር መግለጫ ይሰጣል ተብሏል።
በተያያዘ ዜና
ቅዱስ ሲኖዶስ ከደቂቃዎች በኋላ መግለጫ እንደሚሰጥ ቤተክርስቲያኗ አሳውቃለች።
ዛሬ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩን ጨምሮ አበው ሊቃነ ጳጳሳትን ያካተተ ልኡክ በቤተ መንግሥት ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር ውይይት አካሂደዋል።
ይህን በተመለከተ ቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ ይሰጣል ተብሏል።
ምንጭ፡-ማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት