
ልክ የዛሬ 10 ዓመት፣ በዕለተ ሐሙስ እኤአ ጥቅምት 03/2013፣ 368 ኤርትራውያን ስደተኞች በጣልያኗ የላምፔዱዛ የባሕር ዳርቻ ላይ በደተሰ የጀልባ አደጋ እንደወጡ ቀርተዋል። ይህ አሰቃቂ አደጋ የበርካታ ወጣቶችን ሕይወት ቀጥፏል። አደጋው በሜዲትራኒያን ባሕር ላይ በርካቶች በአሰቃቂ ሁኔታ ካለቁባቸው መካከል በቀዳሚነት ይጠቀሳል። ከዚህ አደጋ በተአምር ተረፍን የሚሉ ሰዎች ትውስታቸውን ለቢቢሲ አውግተዋል።
Source: Link to the Post