የጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ‘የመደመር ትውልድ’ መፅሐፍ ተመረቀ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከዚህ ቀደም ‘መደመር’ እና ‘የመደመር መንገድ’ የተሰኙ ሁለት መፅሐፍትን ለንባብ ማብቃታቸው ይታወሳል።
በዛሬው ዕለት የተመረቀው ‘የመደመር ትውልድ’ በአማርኛ፣ ኦሮምኛ እና እንግሊዘኛ ቋንቋዎች የታተመ ነው።
በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የታደሙ ሲሆን የተለያዩ ምሁራን በመፅሐፉ ላይ ምሁራዊ ዳሰሳ አቅርበዋል።
ዛሬ ከተመረቀው ‘የመደመር ትውልድ’ መጽሀፍ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በየክልሉ የሚገኙ ታሪካዊና የቱሪስት መስህብ የሆኑ ስፍራዎችን ለማደስ እንደሚውል ታውቋል።
ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን
መጋቢት 09 ቀን 2015 ዓ.ም