
በየዓመቱ ጥር 11 የሚከበረው የጥምቀት በዓል በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በደማቅ ሁኔታ እየተከበረ ነው። ከጥምቀት በዓል ዕለት ቀደም ብሎ ባለው ቀን በሚከበረው የከተራ በዓል ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ታቦታት በመውጣት የጥምቀት በዓል ወደሚከበርባቸው ቦታ በሕዝብ ታጅበው ይጓዛሉ። በዚህም መሠረት ጥር 10 ቀን ከፍተኛ ሕዝብ በሚታደምባቸው በተለያዩ የአገሪቱ ከተሞች በተለይም በአዲስ አበባ እና በጎንደር በርካታ ሕዝብ ታድሞባቸዋል።
Source: Link to the Post