“ይቅርታ ስናደርግ ካለፉት ስህተቶች ተምረን እንዳይደገሙ ከልብ በመስራት መሆን አለበት “ሲሉ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ጥሪ አቀረቡ።
–
ፕሬዝዳንቷ ይህን ያሉት የይቅርታ ቀን ሆኖ እየተከበረ ባለው የጳጉሜን አንድ እለትን አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕክት ነው።
–
እለቱ የሃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎችና ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት በይፋ ይቅር በመባባል ተጀምሯል።
–
ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ በዚህ ወቅት “በ2012 ዓ.ም በርካታ መልካምና የሚያኮሩ ተግባራትን እንዲሁም ሊደገሙ የማይገባቸው መጥፎ ጊዜያትን አሳልፈናል” ብለዋል።
–
መጪው አዲስ ዓመትም ለመልካም ሥራዎቻ እውቅና ሰጥቶ ማጠናከር የሚቻልበት እንዲሁም ከስህተቶች በመማር እርምት የሚወሰድበት መሆን እንዳለበት ነው የገለጹት።
–
ለዚህ ደግሞ በዕለት ተዕለት የህይወት ክንዋኔዎች ውስጥ ይቅርታ ማድረግንም ሆነ መቀበልን መለማማድ እንደሚገባ ፕሬዚዳንቷ መክረዋል።
–
“ነገር ግን ይቅርታ ስናደርግ ለታይታ ሳይሆን ካለፉት ስህተቶቻችን ተምረን እንዳይደገሙ ከልብ በመስራት መሆን አለበት” ሲሉም ገልጸዋል።
–
“አገር ያለ ሰው፤ ሰው ደግሞ ያለ መልካም እሴት ወደፊት መሄድ አይችልም” ያሉት ፕሬዚዳንቷ፣ ከዚህ አንጻር ዜጎች የኢትዮጵያዊያን መገለጫ የሆኑ መልካም እሴቶችን አጥብቀው እንዲዙ ጥሪ አቅርበዋል።
–
በግለሰቦችና መንግስት መቀያየር መልካም እሴቶች ሊዋዥቁ እንደማይገባም ነው የገለጹት።
–
ከመልካም እሴቶች ዋነኛው የሆነው ‘ይቅርታ’ የአብሮነትና የጋራ ፍላጎት መገንቢያ መሳሪያ መሆኑንም ፕሬዚዳንቷ ተናግረዋል።
–
ወጣቱን ትውልድ በመልካም እሴቶች መገንባት ከቻልን “አገር ትውደም ብሎ ሳይሆን ለአገር ጠበቃ ሆኖ በአደባባይ ይቆማል” ነው ያሉት።
–
ዛሬን ጨምሮ አምስቱ የጳጉሜን ቀናት የኢትዮጵያን መልካም እሴቶች የሚያጎለብቱ ስያሜዎች ተሰጥቷቸው በተለያዩ ተግባራት እንደሚከበሩ
Source: Link to the Post