
በላይቤርያ በተደረገው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ፕሬዝዳንት ጆርጅ ዊሃ በጠባብ የድምጽ ልዩነት ተሸንፈዋል፡፡
የቀድሞው ታዋቂ የእግር ኳስ ተጫዋች ጆርጅ ዊሃ በሕዝብ ተመርጠው ባለፉት አምስት ዓመታት ላይቤሪያን በፕሬዝዳንትንት ሲመሩ ቆይተዋል።
ለሁለተኛ የሥልጣን ዘመን የተፎካከሩት ፕሬዝዳንት ዊሃ በተቃዋሚ ፓርቲ መሪው ጆሴፍ ቦአካይ በመሸነፋቸው በመጪው ጥር ሥልጣን ያስረክባሉ።
ፕሬዝዳንቱ ለአገሪቱ ሕዝብ ባደረጉት ንግግርም “ላይቤሪያውያን ማንን እንደሚፈልጉ ተናግረዋል፣ እኛም ድምጻቸውን ሰምተናል” በማለት የምርጫውን ውጤት እንደሚቀበሉት አሳውቀዋል።
የተቃዋሚ ፓርቲው ዕጩ ጆሴፍ ቦአካይ ከተቆጠሩት ድምጾች መካከል በ28,000 ድምጽ በሥልጣን ላይ ያሉትን ፕሬዝዳንት ዊሃን በመምራት ነው አሸናፊ መሆናቸው የታወቀው።
ፕሬዝዳንት ዊሃ ሽንፈታቸውን በጸጋ መቀበላቸውን ባሳወቁበት የአምስት ደቂቃ ንግግር “አገራችንን የሚጠቅማትን ይህንን ዴሞክራሲያዊ ሂደት አከብራለሁ” በማለት ተመራጩ ፕሬዝዳንት ካሏቸው አሸናፊው ጆሴፍ ቦአካይ ጋር መነጋገራቸውንም ገልጸዋል።
ላይቤሪያ ከ20 ዓመታት በፊት እጅግ ከባድ እና ለረጅም ጊዜ የዘለቀ የእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ መቆየቷ ይታወቃል።
አሁን በላይቤሪያ የተካሄደው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ከእርስ በርስ ጦርነቱ ማብቃት በኋላ የተደረገ አራተኛው ሲሆን፣ ከባድ ፉክክር እና በጠባብ ውጤት የተጠናቀቀ ምርጫ ነውም ተብሏል።
በሔኖክ ወ/ገብርኤል
ህዳር 10 ቀን 2016 ዓ.ም
ለታማኝና ወቅታዊ መረጃዎች ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ።
Telegram https://t.me/ethiofm107dot8
YouTube
https://www.youtube.com/…/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/video
Source: Link to the Post