
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በፍርድ ቤት ነጻ ተብሏል። አማራ ሚዲያ ማዕከል/አሚማ የካቲት 29 ቀን 2015 ዓ/ም አዲስ አበባ ሸዋ የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝን ጉዳይ ሲያዩት የነበሩት የሕገ-መንግሥት እና የሽብር ወንጀል ችሎት ዳኞች የካቲት 29/2015 በነበረው ችሎት ነጻ መሆኑን በማረጋገጥ አሰናብተውታል። ጋዜጠኛ ተመስገን እንደተናገረውም “በሀገሬ ፍትሕ ሥርዓት ጨርሼ ተስፋ እንዳልቆርጥ ያደርጉ ዳኞች ናቸውና በእጅጉ አመሰግናለሁ” ስለማለቱም ወንድሙ ታሪኩ ደሳለኝ አጋርቷል። ጠበቃ ሄኖክ አክሊሉ እና ቤተ ማርያም አለማየሁም ከእውነት ጎን በመቆም ላደረጉት ትግል እጅግ ተመስግነዋል።
Source: Link to the Post