
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ለከፍተኛ የመንግስት ኃላፊነት ቦታዎች ሹመቶች ሰጡ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 74(2) መሰረት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሚከተሉትን ሹመቶች እንዲያጸድቅ ጠይቀዋል፡፡
በዚህም መሰረት፦
1. ዶክተር ዓለሙ ስሜ – የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር፣
2. ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኝ – የማዕድን ሚኒስትር፣
3. ዶክተር ግርማ አመንቴ – የግብርና ሚኒስትር እንዲሆኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ምክር ቤቱን ጠይቀዋል፡፡
እንዲሁም ከጥር 10 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ
1. አቶ ማሞ ምሕረቱ – የብሔራዊ ባንክ ገዢ፣
2. ወይዘሮ አለምፀሐይ ጳውሎስ – የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ኃላፊና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር፣
3. ዲያቆን ዳንኤል ክብረት – የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማኅበራዊ ዘርፍ አማካሪ ሚኒስትር፣
4. አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ – የጠቅላይ ሚኒስትሩ የውጭ ፖሊሲ አማካሪ ሚኒስትር እና
5. አቶ መለሰ አለሙ – በሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ የዘርፍ አስተባባሪ ሆነው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ተሹመዋል፡፡
Source: Link to the Post