ፉድ ዞን የእሳት አደጋ ደረሰበት።
በቦሌ ክፍለ ከተማ ሰላም ሲቲ አጠገብ የሚገኘው ፉድ ዞን የእሳት አደጋ ደርሶበታል።
የእሳት አደጋው የደረሰው ጥቅምት 8 ቀን 2016 ዓ.ም ምሽት 5፡00 ሰአት አካባቢ ሲሆን የአደጋው መንስኤ ለጊዜው አልታወቀም።
የእሳት አደጋው እንዳይዛመት የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች እና የአዲስ አበባ ፖሊስ ከአካባባቢው ነዋሪዎች በጋራ በመሆን ሊቆጣጠሩት ችለዋል።
እስካሁን ድረስ በአደጋው ምክንያት በሰው እና በንብረት ላይ የደረሰው ውድመት አልታወቀም።
ኢትዮ ኤፍ ኤም በማለዳ ዜናው ስለ አደጋው ተጨማሪ መረጃ የሚያቀርብ ይሆናል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
ጥቅምት 8 ቀን 2016 ዓ.ም