
ፌዴራል ፖሊስ አቶ ስንታየሁ ቸኮልን የት እንዳደረሰው መልስ እንዲሰጥ በፍ/ቤት ታዘዘ። አማራ ሚዲያ ማዕከል/አሚማ የካቲት 27 ቀን 2015 ዓ/ም አዲስ አበባ ሸዋ የልደታ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት መጋቢት ስምንት ሰዓት ተኩል ላይ ፌዴራል ፖሊስ አቶ ስንታየሁ ቸኮልን የት እንዳደረሰው መልስ እንዲሰጥ ታዟል። መጋቢት 12/2015 ደግሞ ፌዴራል ፖሊስ ቀርቦ እንዲከራከር ትእዛዝ ሰጥቷል። ጠበቃ አቶ ታለማ “ደንበኛዬ አቶ ስንታየሁ ቸኮል የት እንዳደረሱት አላውቅም ሃያ ስድስት ቀን አልፎታል፤ ፍርድ ቤትም መቅረብ አልቻለም” የሚል አቤቱታ አቅርበዋል። ፌዴራል ፖሊስ የፍርድ ቤቱን መጥሪያ አልቀበልም ብሎ ጠበቃውን እንዳጉላላቸውም ተገልጧል። በመጨረሻም ጉዳዩን የተከታተለው የልደታ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤትም ፌዴራል ፖሊስ አቶ ስንታየሁ ቸኮልን የት እንዳደረሰው መልስ እንዲሰጥ ስለመታዘዙ የፅናት ሚዲያ ዘገባ አመልክቷል።
Source: Link to the Post